Popular posts from this blog
የበጋው መብረቅ ይናገራል By Zelalem Kibret
በ15 ዓመት ዕድሜው ጠላትን እፋለማለሁ ብሎ የተነሳ፣ ብዙ ተከታዮችን አፍርቶ ጠላት ሊይዝ ሲያሳድደው ሲያሻው ጭልሞ ጫካ ውስጥ ዛፍ ላይ መሰላል ሰርቶ እየተደበቀ፣ ሲያሻው እንደ ምትሃት በጠላት ፊት እየተንጎማለለ ሀገሩን ነፃ ያወጣ ጎረምሳ፡፡ ጃገማ ኬሉ ! የበጋው መብረቅ ! ድንገት ዱብ ባዩ ! ያው የዘር ፖለቲካ ሀገራችን ውስጥ እንደ አስፈሪ ጡር ተመዞ የሚወጋው እየፈለገ ነው፡፡ – ግማሹ “ኢትዮጵያ የፅድቅ ሀገር ነበረች አሁንም ናት” ሲል – ሌላው “የለም! የለም! የብሄር ብሄረሰቦች አስር ቤት ነበረች አሁን ግን የብሄር ብሄረሰብ ሙዚየምነቷን አረጋግጣለች ይላል፡፡” – ግማሹ “ኢትዮጵያ ወይም ሞት” ሲል ቀሪው ደግሞ “ወዴት! ወዴት! ጎሳየ ለኔ ህይወቴ” ብሎ ጎሳውን በሃሳብ ይደጉማል፡፡ – “የኢትዮጵያ ታሪክ በመደብ ጭቆና የተሞላ ነው” ሲል ‘ማርክሲስት’ ነኝ ባዩ – “አይ ! የቅኝ ግዛት ነበር” ይላል ተገንጣዩ – አስንጣዩ (የደረግን ሀረግ ለመዋስ)፡፡ የሆነ ሁኖ ነጭ እና ጥቁር የታሪክ ትርጓሜ ይሄው እንደ ውርስ ሀጢያት አልወርድ ብሎ እሳቱም እየጋመ ይገኛል፡፡ እነዚህ ሰዎች ያልተገነዘቡት ምን ይሆን? ሲባል መልሱን እንደ ጃገማ ኬሎ አይነት አኩሪ ጀግኖች ናቸው ሊመልሱት የሚችሉት፡፡ ጀነራል ጃገማ “ነጭ ጤፍ ከጥቁር እንደማይለይ ኢትዮጵያዊያንን ማለያየት አይቻልም!” በሚል ርዕስ በ1986 “ኢትዮጵያዊነት” የተባለ ድርጅት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ያደረጉት ንግግር፡፡ እነሆ ፡ የኢትዮጵዊነት አላማ በኔ አሰተያየት፡- የኢትዮጵያ አንድነት እና ነፃነት እኩልነት ከተጠበቀ በተፈጥሮ ሃብት የተደላደለች በታሪኳ የነነች ኢትዮጵያ ሳትከፋፈል እና ሳትቆራረስ ለዘላለም እንድትኖር የጎሳ ልዩነት ሳይ...
ሐተታ አድዋ በ በእውቀቱ ስዩም
የአድዋ ድልን ከድንበር ሉአላዊነት ጋር አያይዞ መተንተን የተለመደ ነው፡፡ ድሉ አነሠ በዛ የሚለው ጭቅጭቅ ከዚህ መሠረት ይፈልቃል፡፡ በኔ ግምት የአድዋ ድል ትልቅ ጭብጥ ‹‹የሰውነት ክብር›› ይሰኛል፡፡ ቀደምቶቻችን ወደ አድዋ የጋለቡት በግፍ የተነጠቁትን የሰውነት መታወቂያ ለማስመለስ ነው፡፡ እንዲያውም ሰው መሆናቸውን በማያዳግም መንገድ ያረጋገጡት አድዋ ላይ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ወገኖቼ!! ሰው መሆንን ማረጋገጥ ቀላል ነገር አይምሰላችሁ፡፡ አባቶቻችን ከአውሮፓውያን ጋር የሚጋሩትን ግን ደግሞ ከአውሮፓውያን ቀድመው የሚያውቁትን ቅዱስ መጽሐፍ ጠቅሰው ሁላችንም ያዳም ልጆች ነነ ይሉ ነበር፡፡ እና ያዳም ልጆች ነነ ብለው የሚያምኑ ፈረንጆች ቢቸገሩ የሚደርሱላቸው፣ ቢጠቁ የሚታደጓቸው ወንድሞቻቸው እንደሆኑ ያስቡ ነበር፡፡ በርግጥም የሃይማኖት አንድነት የቀለም ልዩነትን ደምስሶ አዳማዊ ወንድማማችነትን ያስገኘበት የዘመን ምዕራፍ ነበር፡፡ ክርስቶፈር ደጋማ የተባለ የፖርቹጋል ነፍጠኛ ለኢትዮጵያ ደሙን ያፈሰሰው የማተብ አንድነት ስለገፋፋው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ባንድ ወቅት የሚያገለግል የኑሮ ዋስትና በሌላው ዘመን አያገለግልም፡፡ ሁላችንም ያዳም ልጆ ነነ የሚለው የዝምድና ውል ከእለታት አንድ ቀን ያገልግሎት ዘመኑ አለቀ፡፡ በ1548 ተወልዶ በ1600 እንደጧፍ የተቃጠለው ዦርዳኖ ቡርኖ የተባለ የጣልያን መናፍቅ ‹‹ኢትዮጵያውያን ያዳም ልጆች አይደሉም፤ ቅድመ-አዳማዊያን ናቸው እንጂ›› ብሎ ፃፈ፡፡ በቡርኖ ዘመን ኢትዮጵያ የጥቁር ዘር ሁሉ የወል ስሙ ነው፡፡ ቅድመ አዳማዊ ማለት ደሞ በአዳምነት ማዕረግ ያልደረሠ ጅምር ፍጡር ማለት ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ ጥቁሮች በእግዜር አምሳል የተፈጠሩ አይደሉም የሚል ድምዳሜ ላይ ያደርሳል፡፡ ያለማለዘቢያ ለመግለፅ፣ ጥቁሮች ከእንሥሣትና...
Comments
Post a Comment